ከቃል በላይ ለእራስህ፣ ለህሊናህ ታመን!
፨፨፨፨፨፨፨፨/////////////፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ዋናው ጉዳይ ማን ቃል ገባ የሚለው ሳይሆን ማን አብሮ ቆየ፣ ማን አዛለቀ፣ ማን ታመነ የሚለው ነው።
ስንት ቃሉን እንደ እዳና እስር የሚቆጥር ባለበት ዘመን፣ ቃል ሳይገባ፣ መታሰሩን ሳይፈልገ ፍቅሩን ከቃልኪደን አስበልጦ አራሱን የሰጠ፣ ግፊትን ሳያሻ፣ ጫናን ሳይፈልግ በእራሱ የሚታመን ግሩም ሰው አለ።
አዎ! ጀግኒት..! ቃልን እንደ እምነት እስር ከቆጠርሽው መቼም ልባዊ እምነትን አታገኚም። ማንም ሰው እስከጥግ የሚታመንልሽ ቃል ስለገባልሽ፣ በቃሉ ተገዶ ሳይሆን ስለሚወድሽ፣ ስለሚያፈቅርሽና ስለሚያከብርሽ ብቻ ነው።
አዎ! ሰውን በቃል ሳይሆን በፍቅር እሰሪው፣
በግድ ሳይሆን በውድ አስገዢው፣
በጫና ሳይሆን በፍላጎቱ ማርኪው፤
ማንኛውም ሰው የሚያመዛዝን ህሊና አለው፣ የትኛው ትክክል የትኛው ስህተት እንደሆነ ጠንቅቆ ያውቃል።
መታመን እንዳለበት ውስጡ ይነግረዋል፤
መቆጠብ እራሱን መወሰን እንዳለበት ያውቃል፤
አለመታመን ስሜቱን እንደሚጎዳ ያውቃል፤
ከቃል በላይ ህሊናው፣ ፍቅሩ እንደሚያስረው ነጋሪ አያሻውም፤
አዎ! ጀገናዬ..! ቃልን ማክበር፣ መታመን ከባድ ሆኖ አይደለም፣ ካልፈለገና ካላመነበት ግን ሳይከብደው በቀላሉ እምነቱን ያጣል፣ ቃሉን ያጥፋል፣ ስህተት መሆኑ እየገባው ስህተት ይሰራል።
አዎ! በመታመንህ ወቅት እምነትህ ለሰው ሳይሆን ለእራስህ፣ ለገዛ ህሊናህ ነው።
ላለመታመንህ ግዴታ ሌላ ከሳሽ አያስፈልግህም፣ ለወቀሳና ለትቺት የእራስህ ህሊና አያስቀምጥህም። ምናልባት በብዛቱ ልክ ህሊናህም ሊለምደውና ዝም ሊልህ ይችላል፣ ሲነሳ ግን ሊያጠፋህ እንደሚችል እወቅ። የጥፋተኝነት ስሜትን ማስቀረትም ሆነ ማጥፋት የምትችለው፦
ከቃልህ በላይ ለህሊናህ ስትታመን ነው፤
ከሰዎች ይልቅ ለእራስህ ስትታመን ነው፤
ማንም ዘወትር አንተን የሚጠብቅ፣ እግር በእግር የሚቆጣጠር አካል የለም፤ ገዢህም፣ አዛዥህም የገዛ ህሊናህ ነው። ከእርሱ ያመለጥክ እንደሆነ ማቆሚያህ ከባድ ይሆናል፣
ማመዛዘን ትችላለህ፣
መምረጥ ትችላለህ፣
መወሰን፣ ማድረግ ትችላለህና ሁሌም በታማኝነት ተመላለስ፣ ቃል ካለህ ቃልህን ኑር እርሱን ባይኖርህም ህሊናህን አሳርፍ፣
አዎ! ከቃል በላይ ለእራስህ፣ ለህሊናህ ታመን! በጥቂቱ መታመንህ በብዙ ያሾምሃል፣ ትርፍህም ይበዛል፣ ሰላምህም ይፈካል፣ ፍቅርህም ያብባል።
ብሩህ ቀን ይሁንልን! 🏞🌞🌅
ምክረ-አዕምሮ ለተሻለ ነገ! 🦋
Popular posts from this blog
የግዕዝ ምሳሌያዊ አነጋገሮች
የግዕዝ ምሳሌያዊ አነጋገሮች.....#share *ኢይከብር ነቢይ በሀገሩ ነቢይ በሀገሩ አይከበርም። *መዐር አይጥዕሞ ለአድግ ለአህያ ማር አይጥማትም *አድኅን ርእስከ ራስህን አድን *አፍ ይጼውአ ለሞት አፍ ሞትን ይጠራል *ለሰሚዕ እጽብ ለሰሚው አስደናቂ *ብላዕ በሐፈ ገጽከ ጥረህ ግረህ ብላ *አክብር አባከ ወእመከ አባትና እናትህን አክብር *ተፋቀሩ በበይናቲከሙ እርስ በርሳችሁ ተዋደዱ *ኀላፊ ንብረት፣ክመ ጽላሎት ሀብት እንደ ጥላ አላፊ ነው *እምነ ረሃብ የኄይስ ኩይናት ከረሀብ ጦርነት ይሻላል። *ለዘየአምን ኩሉ ይትከሃል ለሚያምን ሁሉ ይቻላል *ሕማማ ለዐይን ርዕየተ ጸላኢ ያይን በሽታዋ ጠላትን ማየቷ *እለ ከርሦሙ አምላኮሙ ሆድ አምላኪዎች *ሀብ ለኩሉ ለዘሰአለከ ለለመነህ ሁሉ ስጥ *በቁስለ ዚአሁ ሀዮነ ቁስለነ በእርሱ ቁስል እኛ ተፈወስን *አኮ ለዘሮጸ ባህቱ ለዘበደረ ለሮጠ አይደለም ለቀደመ እንጅ *አፍቅር ቢጸከ ከመ ነፍስከ ባልንጀራህን እንደራስህ ውደድ *እስመ ፍቅር ከመ ሞት ጽንእት ፍቅር እንደሞት ጽኑ ናት። *ሕይወት ወሞት ውስተ እደ ልሳን ህይወትም ሞትም በአፍ ይመጣሉ *መኑ ከመ አምላከነ? እንደ እግዚአብሔር ያለ ማን አለ? *አኮ በሲበት አላ በአእምሮ በሽበት አይደለም፤በማስተዋል እንጅ *ህብ ፍኖተከ ለእግዚአብሔር መንገድህን ለእግዚአብሔር አደራ ስጥ *ሀቡ ዘነጋሢ ለነጋሢ፤ወዘተረፈእግዚአብሔር ለእግዚአብሔር የቄሳርን ለቄሳር፤የእግዚአብሔርን ለእግዚአብሔር ስጡ። ...
❤️ከአቅምህ በላይ በሆኑ ነገሮች ራስህን አታስጨንቅ። ❤️የጎደለህ ምንድን ነው? ያለህስ ምንድን ነው ? ብታመዛዝነው የቱስ ይበልጣል? መለወጥ የምትችላቸውን ዛሬ ጀምር። መለወጥ የማትችላቸውን ነገሮችን ግን ተቀበላቸው። ❤️አንዳንዴ ሰዎች ጭንቀት ውስጥ የሚገቡት መለወጥ የማይችሏቸውን ነገሮች ለመለወጥ ስለሚጥሩ ነው አታስመስል! ሌሎችን ለምምሰል በመጣር ራስህን አትጣ። ❤️ራስህን መሆን ነፃ ያድርጋል ከራስህ ጋር ሰላም ፍጠር። ራስህንም ከፍ ከፍ አድርገው እችላለሁ አደርገዋለሁ በል አንተ በገዛ እራስህ ካላመንክ ህይወትህ ምንም ዋጋ የለውም!! በምትችለው ሰዎችን እርዳ,,,አመስጋኝ ሁን መልካም ሰዎችን አመስግናቸው። ሁሌም አዲስ ቀን ሲሰጥህ ፈጣሪህንም ማመስግን አትርሳ።
Comments
Post a Comment