የግዕዝ ምሳሌያዊ አነጋገሮች


የግዕዝ ምሳሌያዊ አነጋገሮች.....#share

*ኢይከብር ነቢይ በሀገሩ   
 ነቢይ በሀገሩ አይከበርም።

*መዐር አይጥዕሞ ለአድግ 
ለአህያ ማር አይጥማትም

*አድኅን ርእስከ             
 ራስህን አድን

*አፍ ይጼውአ ለሞት       
 አፍ ሞትን ይጠራል

*ለሰሚዕ እጽብ
ለሰሚው አስደናቂ

*ብላዕ በሐፈ ገጽከ
ጥረህ ግረህ ብላ

*አክብር አባከ ወእመከ
አባትና እናትህን አክብር

*ተፋቀሩ በበይናቲከሙ
እርስ በርሳችሁ ተዋደዱ

*ኀላፊ ንብረት፣ክመ ጽላሎት
ሀብት እንደ ጥላ አላፊ ነው

*እምነ ረሃብ የኄይስ ኩይናት
ከረሀብ ጦርነት ይሻላል።

*ለዘየአምን ኩሉ ይትከሃል
ለሚያምን ሁሉ ይቻላል

*ሕማማ ለዐይን ርዕየተ ጸላኢ
ያይን በሽታዋ ጠላትን ማየቷ

*እለ ከርሦሙ አምላኮሙ
ሆድ አምላኪዎች

*ሀብ ለኩሉ ለዘሰአለከ 
ለለመነህ ሁሉ ስጥ

*በቁስለ ዚአሁ ሀዮነ ቁስለነ
በእርሱ ቁስል እኛ ተፈወስን

*አኮ ለዘሮጸ ባህቱ ለዘበደረ
ለሮጠ አይደለም ለቀደመ እንጅ

*አፍቅር ቢጸከ ከመ ነፍስከ
ባልንጀራህን እንደራስህ ውደድ

*እስመ ፍቅር ከመ ሞት ጽንእት
ፍቅር እንደሞት ጽኑ ናት።

*ሕይወት ወሞት ውስተ እደ ልሳን
ህይወትም ሞትም በአፍ ይመጣሉ

*መኑ ከመ አምላከነ?
እንደ እግዚአብሔር ያለ ማን አለ?

*አኮ በሲበት አላ በአእምሮ
በሽበት አይደለም፤በማስተዋል እንጅ

*ህብ ፍኖተከ ለእግዚአብሔር
መንገድህን ለእግዚአብሔር አደራ ስጥ

*ሀቡ ዘነጋሢ ለነጋሢ፤ወዘተረፈእግዚአብሔር ለእግዚአብሔር
የቄሳርን ለቄሳር፤የእግዚአብሔርን ለእግዚአብሔር ስጡ።

*ሰለአሐዱ በከመ ምግባሩ
ሥራ ለሠሪው እሾህ ላጣሪው (ለእያንዳንዱ እንደሥራው)

*መኑ ዘደመሮ ለብርሃን ምስለ ጽልመት?
ብርሃን ከጨለማ ጋር ምን ኅብረት አለው?

*ማየ ብዙኅ ኢይክል አጥፍአታ ለፊቅር
ብዙ ውሃ ፍቅርን አያጠፋትም

*መጥወኒ እመጥወከ
ስጠኝ እሰጥሃለሁ (እከክልኝ ልከክልህ)

*ሰብእ ወጣኒ፣እግዚአብሔር ፈጻሚ
ሰው ይጀምራል፣እግዚአብሔር ይፈጽማል

*ቀዳሚሃ ለጥበብ ፈሪሃ እግዚአብሔር
የጥበብ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት ነው።

*ብእሲት አዛል (እዚዝ) እክሲል ለምታ
መልካም ሴትን ለባሏ ዘውድ ናት

*አልቦ ዘይእህዝ እርፈ ወየሐርስ ድኅሪተ
ዕርፍ ይዞ ወደ ኋላ የሚያርስ የለም።

*አንፄዋ ለኅልፈታ አንፈ ሄሴሜት ታጼኑ
አይጥ ለሞቷ የድመት አፍንጫ ታሸታለች

*እም ተናግሮ ይኄይስ አርምሞ
ከመናገር ዝም ማለት ይሻላል (ዝምታ ወርቅ ነው)

Comments

Popular posts from this blog