ምድርን ከአደጋ መጠበቅ ይፈልጋሉ
**********************************
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አሁን ያለንበትን የአየር ጠባይ ለውጥ እንደዋዛ መመልከት እንደማገባ በተደጋጋሚ ይገልፃል፡፡ የአየር ጠባይ ለውጡ በአለማችን ታይተው የማይታወቁ ተፈጥሯዊ አደጋዎችን ከማስከተሉም በተጨማሪ ከፍተኛ የሆነ የምግብ ምርት ማነስን ሊያስከትል ይችላል፡፡ የውሀ አካላት ከልካቸው በማለፍ በየአካባቢው የጎርፍ አደጋን እያስከተሉ ይገኛሉ፡፡ በመሆኑም ሀገራት ይህ የተፈጥሮ መናጋት ወደማይመለስበት ደረጃ ከመድረሱ በፊት አስቸኳይ እርምጃን መውሰድ ይኖርባቸዋል፡፡ መንግስታት መስራት ያለባቸውን እስኪሰሩ ድረስ እያንዳንዱ ሰው በግለሰብ ደረጃ የሚኖርባትን ምድር መንከባከብ የሚችልበትን መንገድ ከዚህ እንደሚከተለው ልናስነብባችሁ ወደድን፡፡ መልካም ንባብ
1ኛ. ውሃን በአግባቡ መጠቀም
ስናያቸው ትንሽ ናቸው ብለን የምናስባቸው ነገሮች በትኩረት መሰራት ከቻሉ ትልቅ ለውጥ ማምታት ይችላሉ፡፡ በማንናውም ሰዓት ለምሳሌ ምሳ ለመብላት እጅ ስንታጠብ ወዲያው የመታጠቢያውን ውሀ መዝጋት ከቻልን እና ሌሎችም ይህን እንዲያደርጉ ከገፋፋን በቀላሉ የውሀ ብክነትን መቀነስ እንችላለን፡፡ በእርግጥ ውሃ የሚባክንበት ምክንያት ይህ ብቻ አይደለም፡፡ ሁልጊዜም ቢሆን አንድን ነገር ለመስራት የሚያስፈልገንን ውሃ ብቻ መጠቀም ይኖርብናል፡፡ በተቻለ መጠን ውሀን ከቤታችን እያጣራን እንጠቀም፡፡ በዚህ ምክንያት ምድራችንን ከፕላስቲክ ኮዳዎች መታደግ እንችላለን፡፡
2ኛ. መኪና የመጠቀም ልምዳችንን እንቀንስ
በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ መኪና ይዞ መውጣት ጊዜያዊ የጤና ችግር ከማስከተሉ በተጨማሪ የካርቦን ልቀትን በማስፋፋት የተፈጥሮን ሚዛን ያዛባል፡፡ ከተቻለ ለ2 ቀን ከመኪና መንገድ ራቁ፡፡ መኪና መጠቀም አስፈላጊ ከሆነ ደግሞ በአንድ ጉዞ ብዙ ተጋባራትን በመከወን ምልልሳችንን እንቀንስ፡፡
3ኛ. መራመድ፣ ብስክሌት መጠቀም፣ የህዝብ ትራንስፖርት መጠቀም
በእግር መራመድና ብስክሌት መጠቀም ከተፈጥሮ ጋር ወደር የሌለው ስምምነት አላቸው፡፡ ካልሆነ ደግሞ የህዝብ ትራንስፖርን በመጠቀም በመንገድ ላይ የሚታዩ መኪኖችን ቁጥር በመቀነስ ሀላፍነትን መወጣት አስፈላጊ ነው፡፡
4ኛ. መቀነስ፣ በድጋሚ መጠቀምና ለሌላ አገልግሎት ማዋል
ቆሻሻን በአግባቡ በማስወገድ ብክለትን በከፍተኛ መጠን መቀነስ ያቻላል፡፡ የተጠቀምናቸውን ነገሮች ከማስወገዳችን በፊት በድጋሚ መጠቀም መቻልና አለመቻላችንን ማረጋገጥ፡፡ በድጋሚ መጠቀም ከቻልን እናድርገው፡፡ ካልሆነ ደግሞ ወደሌላ አገልግሎት ለመቀየር ጥረት እናድርግ፡፡ ይህን በማድረግ የሚጣሉና በካይ የሆኑ ነገሮችን መቀነስ እንችላለን፡፡
5ኛ. ቆሻሻን ወደ ተፈጥሮ ማዳበሪያ መቀየር
መበስበስ የሚችሉ ውጋጆችን ጉድጓድ ቆፍሮ በመቅበር ወደተፈጥሮ ማዳበሪያነት መቀየር ይቻላል፡፡ ይህንም ማድረግ በሁለት መልኩ ይጠቅማል፡፡ የመጀመሪያው በአካባቢ የሚታይን ቆሻሻ ይቀንሳል፡፡ ሌላው ደግሙ ለሰብል ልማት የተፈጥሮ ማዳበሪያ የመጠቀም ልምድ እንዲኖር ያደርጋል፡፡
6ኛ. የሐይል አጠቃቀምን ማስተካከል
የምንጠቀመው የቤት ውስጥ አምፖል የሀይል ፍላጎታችንን ይወስነዋል፡፡ በመሆኑም የቤት ውስጥ መገልገያዎቻችንን በሙሉ ሀይል ቆጣቢ በሆኑ መገልገያዎች በመተካት የሀይል ፍጆታችንን እንቀንስ፡፡ የሀይል ፍጆታን መቀነስ ለሀይል የምናወጣውን ወጭ ይቀንስልናል፡፡
7ኛ. ቤታችንን ማስተካከል
ቤታችን በቂ የሆነ ብርሀን የማያስገባ ከሆነ የሀይል ፍላጎታችን ሊጨምር ይችላል፡፡ ስለዚህ ቤትን በቂ ብርሀን እንዲያገኝ ማድረግ በጣም ጠቃሚ ነው፡፡
8ኛ. ለተፈጥሮ ምቹ የሆነ አመጋገብ
በተቻለ መጠን በምርት ሂደት መሬትን የማይጎዱ የግብርና ምርቶችን ለምግብነት መጠቀም በጣም አስፈላጊ ነው፡፡ ከዚህ በበለጠ ደግሞ የጓሮ አትክልትን በራስ አምረቶ መጠቀም ከፍተኛ አስተዋጽኦ አለው፡፡
9ኛ. ዛፎችን መትከልና መንከባከብ
በ2018 የተባበሩት መንግስታት በአየር ንብረት ዙሪያ የሚሰራ የመንግስታት ጥምረት ባወጣው ሪፖርት በ2050 የተለያ ብዛት ያላቸው የተለያዩ የዛፍ ዝርያዎች መተከል አለባቸው ብሎ እየተንቀሳቀሰ ነው፡፡ በሀገራችንም በዚሁ ረገድ አበረታች ስራ እየተሰራ መሆኑ ይታወቃል፡፡ እንደ ግለሰብ ግን በአመት ቢያንስ ሁለት ዛፎችን ተክለን ተንከባክበን ብናጸድቅ የሚመጣውን ለውጥ መገመት ቀላል ነው፡፡
10ኛ. ፕላስቲክን አለመጠቀም
ይህ በማደግ ላይ ባሉ ሀገሮች በጣም አስቸጋሪ ቢሆንም በተፈጥሮ ላይ የሚያመጣው ቀውስ ግን በጣም ከፍተኛ ነው፡፡ ስለዚህ ፕላስቲክን ለመገልገያነት ከመጠቀም መቆጠብ ያስፈልጋል፡፡ በተለይ ለአንድና ሁለት ጊዜ አገልግሎት ብቻ የሚውሉ ፕላስቲኮችን ባለመጠቀም ብድራችንን ከፕላስቲክ ቆሻሻ ማላቀቅ ይኖርብናል፡፡
እነዚህን ከላይ የተዘረዘሩትን 10 ነገሮች ሁሉም የአለም ህዝብ መተግበር ቢችል ምድራችን እንዴት ጤናማ ትሆን ይለናል ከwww.howstuffworks ያገኘነው መረጃ፡፡
Popular posts from this blog
የግዕዝ ምሳሌያዊ አነጋገሮች
የግዕዝ ምሳሌያዊ አነጋገሮች.....#share *ኢይከብር ነቢይ በሀገሩ ነቢይ በሀገሩ አይከበርም። *መዐር አይጥዕሞ ለአድግ ለአህያ ማር አይጥማትም *አድኅን ርእስከ ራስህን አድን *አፍ ይጼውአ ለሞት አፍ ሞትን ይጠራል *ለሰሚዕ እጽብ ለሰሚው አስደናቂ *ብላዕ በሐፈ ገጽከ ጥረህ ግረህ ብላ *አክብር አባከ ወእመከ አባትና እናትህን አክብር *ተፋቀሩ በበይናቲከሙ እርስ በርሳችሁ ተዋደዱ *ኀላፊ ንብረት፣ክመ ጽላሎት ሀብት እንደ ጥላ አላፊ ነው *እምነ ረሃብ የኄይስ ኩይናት ከረሀብ ጦርነት ይሻላል። *ለዘየአምን ኩሉ ይትከሃል ለሚያምን ሁሉ ይቻላል *ሕማማ ለዐይን ርዕየተ ጸላኢ ያይን በሽታዋ ጠላትን ማየቷ *እለ ከርሦሙ አምላኮሙ ሆድ አምላኪዎች *ሀብ ለኩሉ ለዘሰአለከ ለለመነህ ሁሉ ስጥ *በቁስለ ዚአሁ ሀዮነ ቁስለነ በእርሱ ቁስል እኛ ተፈወስን *አኮ ለዘሮጸ ባህቱ ለዘበደረ ለሮጠ አይደለም ለቀደመ እንጅ *አፍቅር ቢጸከ ከመ ነፍስከ ባልንጀራህን እንደራስህ ውደድ *እስመ ፍቅር ከመ ሞት ጽንእት ፍቅር እንደሞት ጽኑ ናት። *ሕይወት ወሞት ውስተ እደ ልሳን ህይወትም ሞትም በአፍ ይመጣሉ *መኑ ከመ አምላከነ? እንደ እግዚአብሔር ያለ ማን አለ? *አኮ በሲበት አላ በአእምሮ በሽበት አይደለም፤በማስተዋል እንጅ *ህብ ፍኖተከ ለእግዚአብሔር መንገድህን ለእግዚአብሔር አደራ ስጥ *ሀቡ ዘነጋሢ ለነጋሢ፤ወዘተረፈእግዚአብሔር ለእግዚአብሔር የቄሳርን ለቄሳር፤የእግዚአብሔርን ለእግዚአብሔር ስጡ። ...
❤️ከአቅምህ በላይ በሆኑ ነገሮች ራስህን አታስጨንቅ። ❤️የጎደለህ ምንድን ነው? ያለህስ ምንድን ነው ? ብታመዛዝነው የቱስ ይበልጣል? መለወጥ የምትችላቸውን ዛሬ ጀምር። መለወጥ የማትችላቸውን ነገሮችን ግን ተቀበላቸው። ❤️አንዳንዴ ሰዎች ጭንቀት ውስጥ የሚገቡት መለወጥ የማይችሏቸውን ነገሮች ለመለወጥ ስለሚጥሩ ነው አታስመስል! ሌሎችን ለምምሰል በመጣር ራስህን አትጣ። ❤️ራስህን መሆን ነፃ ያድርጋል ከራስህ ጋር ሰላም ፍጠር። ራስህንም ከፍ ከፍ አድርገው እችላለሁ አደርገዋለሁ በል አንተ በገዛ እራስህ ካላመንክ ህይወትህ ምንም ዋጋ የለውም!! በምትችለው ሰዎችን እርዳ,,,አመስጋኝ ሁን መልካም ሰዎችን አመስግናቸው። ሁሌም አዲስ ቀን ሲሰጥህ ፈጣሪህንም ማመስግን አትርሳ።
Comments
Post a Comment