ውልደቱ ጎጃም ሲሆን ለቤተሰቡ አራተኛ ልጅ ነው ። ከውልደቱ ጎጃም ይልቅ ሐመሮች ማርከውታል። በሐመሮች መማረክ ብቻ ሳይሆን በብዕሩ ተከታታይ መጻሕፍት ደርሶላቸዋል። አስጊጦ ጽፎላቸዋል ። ፍቅረማርቆስ ደስታ በሀገራችን የመጀመሪያ የሆነውን በብሔረሰቦች ባህል ላይ ያተኮሩ ተከታታይ መፃህፍትን ያበረከተ ደራሲ ነው። 'ከቡስካ በስተጀርባ'፣ 'ኢቫንጋዲ'፣ 'የዘርሲዎች ፍቅር'፣ 'አቻሜ' ና 'የንሥር ዓይን' የተሰኙት በሐመር ብሔረሰብ ታሪክ ላይ ያተኮሩት መጻሕፍት የብሔረሰቡን ባህል ና ትውፊት ከማስተዋወቁም በላይ የህዝቡን ዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ በድርሰቶቹ ያሳየን ደራሲ ነው ። ፍቅረማርቆስ የሐመር ብሔረሰብን ባህል የማስተዋወቅ ሥራውን አጠናክሮ በመቀጠል ለውጪው ዓለም አንባቢያን የሚሆን ሥራውን በእንግሊዝኛም አሳትሟል ። ይዀው ''Land of the Yellow Bull'' የተሰኘው መጽሐፉ በመላው ዓለም ተሰራጭቷል። 'የበጋው መብረቅ' በጃግማ ኬሎ የህይወት ታሪክ ላይ ያጠነጠነ መጽሐፍም ጽፏል ።
በሀገራችን በመጽሐፍ ታሪክ ውስጥ ቁጥራቸው በከፍተኛ ሁኔታ ታትሞ ለሕዝብ ከቀረቡ መጻሕፍት መካከል የእሱ መጻሕፍት ተጠቃሽ ናቸው ። ከ''መቶ ሺህ'' በላይ መጻሕፍቱ ታትመው ለገበያ ቀርበው ተሽጦለታል ። አምስት መጻህፍቶቹ በገበያ ላይ ሲውሉ ከአንድ በላይ የመታተም ዕድልን አግኝተዋል ። የመጀመሪያ መጽሐፋ [ከቡስካ በስተጀርባ] ሰባት ጊዜ ታትሟል ፤ ሁለተኛው [ኢቫንጋዲ ] አምስት ጊዜ ፣ ሦስተኛው [የዘርሲዎች ፍቅር] አራት ጊዜ ፤ አራተኛው [አቻሜ ] ሁለት ጊዜ ፤ አምስተኛውም[ የንሥር ዓይን] እንዲሁ ሁለተኛ ጊዜ ታትሟል ። ስድስተኛው መጽሐፉን ለየት የሚያደርገው በእንግሊዝኛ መታተሙ ነው ። የሃምሳ ሁለት ዓመቱ ደራሲ ፍቅረማርቆስ ደስታ የራሱን ስራዎች ሰብስቦ በእንግሊዝኛ ሲያሳትም በረዥም ልቦለድ ታሪክ ሶስተኛው ሰው ነው ።
ደራሲው በሐመሮች ባህልና ትውፊት ተማርኮ በባህሉም መሠረት በስጋ ሳይዋለዳቸው የብሔረሰቡ ሙሉ በሙሉ አባል ሆኗል፡፡ ፍቅረማርቆስ በ2011 ዓ.ም ከዘጠኝ ዓመታት ስደት ቆይታ በኃላ ሐመር ሲደርስ ጠፍቶ የመጣ ሰው ከማህበረሰቡ ጋር ለመቀላቀል መገረፍ ስላለበት በሐመር ጎረምሶች ከተገረፈ በኃላ ከማህበረሰቡ ጋር ተቀላቅሏል ። 



Comments

Popular posts from this blog

የግዕዝ ምሳሌያዊ አነጋገሮች