✍️ ትክክለኛው መንገድ ላይ ሳትሆን መሮጥ ትርጉሙ ምንድን ነው?
ሕይወት የእሽቅድድም መድረክ ነው:: በየፊናው ውድድር እና ጥሎ ማለፍ የሞላበት ክስተት ነው::
በትክክለኛው የህይወት ጎዳና ላይ ሳንሆን የምናደረገው እሽቅድድም ግን የማይረባና ትርጉም የሌለው ነው::
ውጤቱም ውድቀት ነው::
ምንም ያክል ረጅም ርቀት ቢኬድም መንገዱ ትክክለኛ ካልሆነ የተሻለ መፍትሄዉ መሮጥ ሳይሆን ወደኋላ መመለስ ነው::
መነሻዉ መድረሻውን የሚወሰነው የህይወት ሩጫ አለ::
ጅማሪው ትክክለኛው ካልሆነ ፍፃሜውም ስህተት ነው::
ለዚህ ደግሞ የተሻለ አማራጭ ትክክለኛ መንገድ መሆኑን ሳናረጋግጥ አለመሮጥ ነው:: የትኛውንም ተግባራዊ እርምጃ ከማድረግ በፊት ማሰብ ማሰላሰል እና መመርመር ያስፈልጋል::
ጥልቅ በሆነ ማሰብና ማሰላሰል ውስጥ ህልውና ንቁ ይሆንና የሚደረገው ተግባራዊ እርምጃ ትክክል መሆን አለመሆኑን ያሳውቃል ::
ይህን ሂደት አልፎ የሚከወን ተግባርም ሙሉ በሙሉ ከስህተት ባይፀዳም ትርጉም ያለው ይሆናል ::
***ብሩህ ጊዜ🙏🙏🙏
Popular posts from this blog
የግዕዝ ምሳሌያዊ አነጋገሮች
የግዕዝ ምሳሌያዊ አነጋገሮች.....#share *ኢይከብር ነቢይ በሀገሩ ነቢይ በሀገሩ አይከበርም። *መዐር አይጥዕሞ ለአድግ ለአህያ ማር አይጥማትም *አድኅን ርእስከ ራስህን አድን *አፍ ይጼውአ ለሞት አፍ ሞትን ይጠራል *ለሰሚዕ እጽብ ለሰሚው አስደናቂ *ብላዕ በሐፈ ገጽከ ጥረህ ግረህ ብላ *አክብር አባከ ወእመከ አባትና እናትህን አክብር *ተፋቀሩ በበይናቲከሙ እርስ በርሳችሁ ተዋደዱ *ኀላፊ ንብረት፣ክመ ጽላሎት ሀብት እንደ ጥላ አላፊ ነው *እምነ ረሃብ የኄይስ ኩይናት ከረሀብ ጦርነት ይሻላል። *ለዘየአምን ኩሉ ይትከሃል ለሚያምን ሁሉ ይቻላል *ሕማማ ለዐይን ርዕየተ ጸላኢ ያይን በሽታዋ ጠላትን ማየቷ *እለ ከርሦሙ አምላኮሙ ሆድ አምላኪዎች *ሀብ ለኩሉ ለዘሰአለከ ለለመነህ ሁሉ ስጥ *በቁስለ ዚአሁ ሀዮነ ቁስለነ በእርሱ ቁስል እኛ ተፈወስን *አኮ ለዘሮጸ ባህቱ ለዘበደረ ለሮጠ አይደለም ለቀደመ እንጅ *አፍቅር ቢጸከ ከመ ነፍስከ ባልንጀራህን እንደራስህ ውደድ *እስመ ፍቅር ከመ ሞት ጽንእት ፍቅር እንደሞት ጽኑ ናት። *ሕይወት ወሞት ውስተ እደ ልሳን ህይወትም ሞትም በአፍ ይመጣሉ *መኑ ከመ አምላከነ? እንደ እግዚአብሔር ያለ ማን አለ? *አኮ በሲበት አላ በአእምሮ በሽበት አይደለም፤በማስተዋል እንጅ *ህብ ፍኖተከ ለእግዚአብሔር መንገድህን ለእግዚአብሔር አደራ ስጥ *ሀቡ ዘነጋሢ ለነጋሢ፤ወዘተረፈእግዚአብሔር ለእግዚአብሔር የቄሳርን ለቄሳር፤የእግዚአብሔርን ለእግዚአብሔር ስጡ። ...
❤️ከአቅምህ በላይ በሆኑ ነገሮች ራስህን አታስጨንቅ። ❤️የጎደለህ ምንድን ነው? ያለህስ ምንድን ነው ? ብታመዛዝነው የቱስ ይበልጣል? መለወጥ የምትችላቸውን ዛሬ ጀምር። መለወጥ የማትችላቸውን ነገሮችን ግን ተቀበላቸው። ❤️አንዳንዴ ሰዎች ጭንቀት ውስጥ የሚገቡት መለወጥ የማይችሏቸውን ነገሮች ለመለወጥ ስለሚጥሩ ነው አታስመስል! ሌሎችን ለምምሰል በመጣር ራስህን አትጣ። ❤️ራስህን መሆን ነፃ ያድርጋል ከራስህ ጋር ሰላም ፍጠር። ራስህንም ከፍ ከፍ አድርገው እችላለሁ አደርገዋለሁ በል አንተ በገዛ እራስህ ካላመንክ ህይወትህ ምንም ዋጋ የለውም!! በምትችለው ሰዎችን እርዳ,,,አመስጋኝ ሁን መልካም ሰዎችን አመስግናቸው። ሁሌም አዲስ ቀን ሲሰጥህ ፈጣሪህንም ማመስግን አትርሳ።
Comments
Post a Comment