←↑↓→
በዚህ ሁሉ መሐል...
አሁንም ሰው አለ፤
አሁንም ሕዝብ አለ - በጽናት የቆመ፤
ሀገር እንዳትወድቅ - እንደተሸከመ፤
(ያውም ክንዱ እስኪዝል፣ ብዙ እየታመመ።)
↑↓↑
ምን የችግር ብዛት፣ ቢወርድ እንደ ናዳ፤
ንፁሃን ቢሰውም፣ ለትውልዱ ዕዳ፤
ጥቂት ብርቱ ካለ፣ በጽናት የሚቆም፤
መቃናቷ አይቀርም፣ ሀገር ምን ብታዘም።
=→
ፈታኝ ወቅትን ማለፍ፣ ቢከብድም ባይከብድም፤
የመስዋዕት ምድር፣ ከከፍታ አትወርድም።
→←
Sewagegn At.
Comments
Post a Comment