"ሰውነት" !
...
"ሕዝበ አዳሜ ሁሉ፣ ሰው እየመሰለ፤
በሰዎች ወንበር ላይ፣ ተቀምጦ የዋለ፤
በሰውነት መስፈርት፣ አሁን ሰው የት አለ?"

ብዬ ለመናገር፣ ምላሴን ሳስዬ፤
ለማውጣት ስጀምር፣ ድምፅ ከጉሮሮዬ፤
"ቆይ ግን አንተስ ሰው ነህ?" አለኝ ሕሊናዬ።
---
ሰውነት ሲከዳ...
ከሰብዓዊ ዓለም፣ ሰይጣን ይወለዳል፤
በመሰይጠን ዘመን፣
ከምንም ከምንም፣ ሰው መሆን ይከብዳል።
-----//-----)

Comments

Popular posts from this blog

የግዕዝ ምሳሌያዊ አነጋገሮች

ግዕዝና አማረኛ ዓለም አቀፍ ናቸው