የአፍንጫ መድማትን ለማቆም የሚያስችል መንገድ
********************************
ምንም እንኳን የአፍንጫ መድማት ወይም ነስር አስደንጋጭ ቢሆንም አብዛኛውን ጊዜ የተለመደ ነው፡፡ በአሜሪካ በተደረገ ጥናት ወደ 60 ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎች የአፍንጫ መድማት ይታይባቸዋል፡፡ በተለይ ከ2-10 ዕድሜ ክልል ያሉ ህፃናትና ከ50-80 ዕድሜ ክልል ያሉ ሰዎች ከፍተኛውን የቁጥር ድርሻ ይወስዳሉ፡፡
አፍንጫችን የምንስበውን አየር የሚያረጥቡ ብዙ የደም ስሮች አሉት፡፡ በአፍንጫችን በኩል የሚገባው አየርም ወደ አፍንጫችን ግድግዳ ተጠግቶ በሚያልፍበት ወቅት ለዚህ የመድማት ችግር ልንጋለጥ እንችላለን፡፡ ይህም የሚሆነው ከፍተኛ ግፊት ያለው ነፋስ ሲኖርና በእጃች አላስፈላጊ መነካካት ስናዘወትር ነው፡፡ እዚህ አካባቢ የሚከሰት መድማት anterior nosebleeds በመባል ይታወቃል፡፡
ብዙ ጊዜ ያልተለመደውና የከፋ ጉዳት ሊያደርስ የሚችለው ከውስጠኛው የአፍንጫ ስር የሚመነጨው posterior nosebleeds የሚባለው ነው፡፡ ልዩ ህክምናም የሚስፈልገው የአፍንጫ መድማትም ይህኛው ነው፡፡ የዚህ አይነቱ የአፍንጫ መድማት በአደጋ የአፍንጫ መሰበር ሲያጋጥም፣ የቅርብ ጊዜ የአፍንጫ ቀዶ ህክምና ሲኖር፣ ደምን ሊያቀጥኑ የሚችሉ መድሀኒቶችን ስንጠቀም፣ የደም ስሮችን የሚጎዳ ተፈጥሯዊ ችግር ሲኖርና የሉኪሚያ ተጠቂ ስንሆን የሚከሰት ነው፡፡
ይሁንና የአፍንጫ መድማትን በቀላሉ በቤት ውስጥ ማሰቆም ይቻላል፡፡ ችግሩን ለማስቆም ብዙ መንገዶች ቢኖሩም በአሜሪካ የሚገኘው Yale Medicine ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ቅደም ተከተሎች መከተል ተገቢ ነው ይላል፡፡
ተስተካክሎ በመቀመጥ የአፍንጫን ለስላሳውን ክፍል በለስላሳ ጨርቅ ወይም በሶፍት ለ10 ደቂቃ ያክል መያዝ
እጅን ፊት ለፊት አድርጎ አፍንጫን መያዝና በአፍ ብቻ መተንፈስ
በጨርቅ የተጠቀለለ በረዶ ከግንባራችን ስር በማድረግ የአፍንቻችን የደም ቧንቧዎች እንዲጠቡ ማድረግ
መተኛት ወይም መንጋለል ልባችንን ወደ አፍንጫችን ስለሚያቀርበው በተቻለ መጠን ተስተካክሎ መቀመጥ
ከላይ የተጠቀሱትን መንገዶች በአግባቡ ከተገበርን መድማቱ የመቆም እድሉ ከፍተኛ ነው፡፡ ነገር ግን ወደ ህክምና ተቋም መሔድ የሚጠበቅብን ጊዜ ሊኖር እንደሚችል ልብ ማለት ያስፈልጋል፡፡ በተለይ Revere Health የተባለ የምርምር ተቋም ወደ ህክምና ሊያስኬዱን የሚችሉ ምልክቶችን እንዲህ ሲል ዘርዝሯል፡፡
ከላይ የተዘረዘሩትን መንገዶች ተጠቅመን የአፍንጫ መድማቱ ካልቆመ
የአፍንጫ መድማቱ የተከሰተው በአደጋ ከሆነ
አፍንጫችን የደማው የደም ማቅጠኛ መድሐኒቶችን ከወሰድን በኋላ ከሆነ
ምንጭ:- www.howstuffworks.com
Popular posts from this blog
የግዕዝ ምሳሌያዊ አነጋገሮች
የግዕዝ ምሳሌያዊ አነጋገሮች.....#share *ኢይከብር ነቢይ በሀገሩ ነቢይ በሀገሩ አይከበርም። *መዐር አይጥዕሞ ለአድግ ለአህያ ማር አይጥማትም *አድኅን ርእስከ ራስህን አድን *አፍ ይጼውአ ለሞት አፍ ሞትን ይጠራል *ለሰሚዕ እጽብ ለሰሚው አስደናቂ *ብላዕ በሐፈ ገጽከ ጥረህ ግረህ ብላ *አክብር አባከ ወእመከ አባትና እናትህን አክብር *ተፋቀሩ በበይናቲከሙ እርስ በርሳችሁ ተዋደዱ *ኀላፊ ንብረት፣ክመ ጽላሎት ሀብት እንደ ጥላ አላፊ ነው *እምነ ረሃብ የኄይስ ኩይናት ከረሀብ ጦርነት ይሻላል። *ለዘየአምን ኩሉ ይትከሃል ለሚያምን ሁሉ ይቻላል *ሕማማ ለዐይን ርዕየተ ጸላኢ ያይን በሽታዋ ጠላትን ማየቷ *እለ ከርሦሙ አምላኮሙ ሆድ አምላኪዎች *ሀብ ለኩሉ ለዘሰአለከ ለለመነህ ሁሉ ስጥ *በቁስለ ዚአሁ ሀዮነ ቁስለነ በእርሱ ቁስል እኛ ተፈወስን *አኮ ለዘሮጸ ባህቱ ለዘበደረ ለሮጠ አይደለም ለቀደመ እንጅ *አፍቅር ቢጸከ ከመ ነፍስከ ባልንጀራህን እንደራስህ ውደድ *እስመ ፍቅር ከመ ሞት ጽንእት ፍቅር እንደሞት ጽኑ ናት። *ሕይወት ወሞት ውስተ እደ ልሳን ህይወትም ሞትም በአፍ ይመጣሉ *መኑ ከመ አምላከነ? እንደ እግዚአብሔር ያለ ማን አለ? *አኮ በሲበት አላ በአእምሮ በሽበት አይደለም፤በማስተዋል እንጅ *ህብ ፍኖተከ ለእግዚአብሔር መንገድህን ለእግዚአብሔር አደራ ስጥ *ሀቡ ዘነጋሢ ለነጋሢ፤ወዘተረፈእግዚአብሔር ለእግዚአብሔር የቄሳርን ለቄሳር፤የእግዚአብሔርን ለእግዚአብሔር ስጡ። ...
ግዕዝና አማረኛ ዓለም አቀፍ ናቸው
ግዕዝና አማረኛ ዓለም አቀፍ ናቸው ስንል ይኸው በማስረጃ ነው። ጥንታዊቷ ፊደላችን ♥ አ ቦ ጊ ዳ ................ የኢትዮጵያ ታሪክ ቅርስ በዓለም ሁሉ የአበራ የተመዘገበ ነው እኛ የእኛውን ሀብታችን እንጠብቅ።ትንሽ ስለአማርኛ ቋንቋ ... መራራ ሃቅ 1. የአማርኛ ቋንቋ ከክርስቶስ ልደት በፊት ነበረ። በሁለተኛው ክፍለ ዘመን (200-130 ዓ . ዓ ) የግብጹ ንጉሥ ጥሊሞስ 7 ኛ መምህር የነበረውና የግሪክ መልክዓ ምድር ተመራማሪ አጋታርከስ በሰሜን ኢትዮጵያ የሚኖሩ ህዝቦች የሚናገሩት የአማርኛ ቋንቋ እንደሆነ ጽፏል፥ተረጋግጧል።በአርኪኦሎጂያዊ ምርመራ ሂደት በአማርኛ የተቀረጹ ጥንታዊ የድንጋይ ላይ ጽሁፎች ተገኝተዋል ( አምሳሉ 1976) 2. አማራዎች ከ 3 ሺህ አመት በፊት በአማርኛ ቋንቋ ለንግሥት ሳባ ልጅ " ምኒልክ " ብለው ስም ከአወጡ በኋላ ይሁን በፊት በርካታ ስሞችን በአማርኛ እናገኛለን። 3. አሜሪካዊው ቤንደር በ 1966 ዓ . ም በኦክስፎርድ ዩኒቨርስቲ ባሳተመው /Language in Ethiopia/ በሚሰኘው መፅሐፉ በ 9 ኛው መቶ ክፍለ ዘመን አማርኛ በቤተ - አምሓራ እንደተስፋፋ ጽፏል።ኩፐር የተባለው ጽሐፊ በንጉስ ላሊበላ ዘመን አማርኛ ከአገወኛ ጋር በህዝቡ ይነገር ነበር ብሏል። 4. በ 12 ኛው መክዘ አጼ ይኩኖ አምላክ ዘመን ዐማርኛ ቋንቋ ፈጽሞ ሠለጠነ ፤ ያማረ የተወደደ ፥ ጉሮሮ የማያንቅ ፥ ለንግግር የማያውክ ሁኖ ስለ ተገኘ ፣ የቤተ መንግሥት ቋንቋ ሆነ።ለአማርኛ ዕድገት የ...

Comments
Post a Comment