የደም እንባ
መስከረም 25 ቀን 2013ዓ.ም
የ15 አመቷ ብራዚላዊት ልጃገረድ ሀኪሞች ሊደርሱበት ባልቻሉበት ሁኔታ ከሳምንት ለበለጠ ጊዜ ከአይኖቿ ደም መፍሰስ እንደጀመረ ኦዲቴ ሴንትራል በሰሞኑ የዜና ገጹ አስነብቧል::
ዶሪስ እ.ኤ.አ መስከረም 12/2020 በመታመሟ ምክንያት እናቷ ሳኦፖሎ ወደ ሚገኘው ሆስፒታል ስትወስዳት የኩላሊት ጠጠር ተብላ መድሃኒት ሰጥተዋት ወደ ቤቷ ተመልሳ ነበር ::በነጋታው ግን ከአንድ አይኗ ደም መፍሰስ በመጀመሩ ድጋሚ ወደ ሆስፒታል ታመራለች፤ ይህን ተከትሎም ዶክተሮች የተለያዩ ምርመራዎችን ቢያካሂዱላትም በምን ምክንያት ከአይኗ ደም ሊፈስ እንደቻለ ማወቅ አልቻሉም::
ምንም አይነት ህመም ስለማይሰማትም ወደ ቤት እንድትሄድ ቢያደርጓትም ከእንደገና ሁለቱ አይኖቿ ድጋሚ ደም ማፍሰስ በመጀመራቸው አሁንም ወደ ሆስፒታል ተወስዳለች:: ይሁንና ዶሪስ ላይ ምን እየተካሄደ እንዳለ ማወቅ አልተቻለም::
የአይን ሃኪም የሆኑት ራፋኤል አንቶኒዮ እንደተናገሩት እንደዚህ አይነት ሁኔታ ሲፈጠር በህክምና ቋንቋ ሄሞላክሪያ ተብሎ ይጠራል:: ህክምናውም እንደተነሳበት ምክንያት ይሰጣል:: አንዳንዴም በራሱ ጊዜ የሚጠፋ በመሆኑ መድሃኒት አያስፈልገውም::
ዶ/ር ሊአንድሮ ፎንሲካ እንደገለጹት ደግሞ ይህ ሁኔታ በህመምተኛው ሰውነት ውስጥ በሚፈጠር ችግር የሚከሰት ሲሆን ለማከምም ያን ያህል ውስብስብ አይደለም:: በጸረ ተህዋሲያንና በሆርሞን ህክምና ይታከማል:: አልፎ አልፎ ግን ሁኔታው ለሌላ የጤና እክል ታማሚውን ሊዳርግ ይችላል::
Popular posts from this blog
የግዕዝ ምሳሌያዊ አነጋገሮች
የግዕዝ ምሳሌያዊ አነጋገሮች.....#share *ኢይከብር ነቢይ በሀገሩ ነቢይ በሀገሩ አይከበርም። *መዐር አይጥዕሞ ለአድግ ለአህያ ማር አይጥማትም *አድኅን ርእስከ ራስህን አድን *አፍ ይጼውአ ለሞት አፍ ሞትን ይጠራል *ለሰሚዕ እጽብ ለሰሚው አስደናቂ *ብላዕ በሐፈ ገጽከ ጥረህ ግረህ ብላ *አክብር አባከ ወእመከ አባትና እናትህን አክብር *ተፋቀሩ በበይናቲከሙ እርስ በርሳችሁ ተዋደዱ *ኀላፊ ንብረት፣ክመ ጽላሎት ሀብት እንደ ጥላ አላፊ ነው *እምነ ረሃብ የኄይስ ኩይናት ከረሀብ ጦርነት ይሻላል። *ለዘየአምን ኩሉ ይትከሃል ለሚያምን ሁሉ ይቻላል *ሕማማ ለዐይን ርዕየተ ጸላኢ ያይን በሽታዋ ጠላትን ማየቷ *እለ ከርሦሙ አምላኮሙ ሆድ አምላኪዎች *ሀብ ለኩሉ ለዘሰአለከ ለለመነህ ሁሉ ስጥ *በቁስለ ዚአሁ ሀዮነ ቁስለነ በእርሱ ቁስል እኛ ተፈወስን *አኮ ለዘሮጸ ባህቱ ለዘበደረ ለሮጠ አይደለም ለቀደመ እንጅ *አፍቅር ቢጸከ ከመ ነፍስከ ባልንጀራህን እንደራስህ ውደድ *እስመ ፍቅር ከመ ሞት ጽንእት ፍቅር እንደሞት ጽኑ ናት። *ሕይወት ወሞት ውስተ እደ ልሳን ህይወትም ሞትም በአፍ ይመጣሉ *መኑ ከመ አምላከነ? እንደ እግዚአብሔር ያለ ማን አለ? *አኮ በሲበት አላ በአእምሮ በሽበት አይደለም፤በማስተዋል እንጅ *ህብ ፍኖተከ ለእግዚአብሔር መንገድህን ለእግዚአብሔር አደራ ስጥ *ሀቡ ዘነጋሢ ለነጋሢ፤ወዘተረፈእግዚአብሔር ለእግዚአብሔር የቄሳርን ለቄሳር፤የእግዚአብሔርን ለእግዚአብሔር ስጡ። ...
❤️ከአቅምህ በላይ በሆኑ ነገሮች ራስህን አታስጨንቅ። ❤️የጎደለህ ምንድን ነው? ያለህስ ምንድን ነው ? ብታመዛዝነው የቱስ ይበልጣል? መለወጥ የምትችላቸውን ዛሬ ጀምር። መለወጥ የማትችላቸውን ነገሮችን ግን ተቀበላቸው። ❤️አንዳንዴ ሰዎች ጭንቀት ውስጥ የሚገቡት መለወጥ የማይችሏቸውን ነገሮች ለመለወጥ ስለሚጥሩ ነው አታስመስል! ሌሎችን ለምምሰል በመጣር ራስህን አትጣ። ❤️ራስህን መሆን ነፃ ያድርጋል ከራስህ ጋር ሰላም ፍጠር። ራስህንም ከፍ ከፍ አድርገው እችላለሁ አደርገዋለሁ በል አንተ በገዛ እራስህ ካላመንክ ህይወትህ ምንም ዋጋ የለውም!! በምትችለው ሰዎችን እርዳ,,,አመስጋኝ ሁን መልካም ሰዎችን አመስግናቸው። ሁሌም አዲስ ቀን ሲሰጥህ ፈጣሪህንም ማመስግን አትርሳ።
Comments
Post a Comment