የደም እንባ
መስከረም 25 ቀን 2013ዓ.ም
የ15 አመቷ ብራዚላዊት ልጃገረድ ሀኪሞች ሊደርሱበት ባልቻሉበት ሁኔታ ከሳምንት ለበለጠ ጊዜ ከአይኖቿ ደም መፍሰስ እንደጀመረ ኦዲቴ ሴንትራል በሰሞኑ የዜና ገጹ አስነብቧል::
ዶሪስ እ.ኤ.አ መስከረም 12/2020 በመታመሟ ምክንያት እናቷ ሳኦፖሎ ወደ ሚገኘው ሆስፒታል ስትወስዳት የኩላሊት ጠጠር ተብላ መድሃኒት ሰጥተዋት ወደ ቤቷ ተመልሳ ነበር ::በነጋታው ግን ከአንድ አይኗ ደም መፍሰስ በመጀመሩ ድጋሚ ወደ ሆስፒታል ታመራለች፤ ይህን ተከትሎም ዶክተሮች የተለያዩ ምርመራዎችን ቢያካሂዱላትም በምን ምክንያት ከአይኗ ደም ሊፈስ እንደቻለ ማወቅ አልቻሉም::
ምንም አይነት ህመም ስለማይሰማትም ወደ ቤት እንድትሄድ ቢያደርጓትም ከእንደገና ሁለቱ አይኖቿ ድጋሚ ደም ማፍሰስ በመጀመራቸው አሁንም ወደ ሆስፒታል ተወስዳለች:: ይሁንና ዶሪስ ላይ ምን እየተካሄደ እንዳለ ማወቅ አልተቻለም::
የአይን ሃኪም የሆኑት ራፋኤል አንቶኒዮ እንደተናገሩት እንደዚህ አይነት ሁኔታ ሲፈጠር በህክምና ቋንቋ ሄሞላክሪያ ተብሎ ይጠራል:: ህክምናውም እንደተነሳበት ምክንያት ይሰጣል:: አንዳንዴም በራሱ ጊዜ የሚጠፋ በመሆኑ መድሃኒት አያስፈልገውም::
ዶ/ር ሊአንድሮ ፎንሲካ እንደገለጹት ደግሞ ይህ ሁኔታ በህመምተኛው ሰውነት ውስጥ በሚፈጠር ችግር የሚከሰት ሲሆን ለማከምም ያን ያህል ውስብስብ አይደለም:: በጸረ ተህዋሲያንና በሆርሞን ህክምና ይታከማል:: አልፎ አልፎ ግን ሁኔታው ለሌላ የጤና እክል ታማሚውን ሊዳርግ ይችላል::
Popular posts from this blog
የግዕዝ ምሳሌያዊ አነጋገሮች
የግዕዝ ምሳሌያዊ አነጋገሮች.....#share *ኢይከብር ነቢይ በሀገሩ ነቢይ በሀገሩ አይከበርም። *መዐር አይጥዕሞ ለአድግ ለአህያ ማር አይጥማትም *አድኅን ርእስከ ራስህን አድን *አፍ ይጼውአ ለሞት አፍ ሞትን ይጠራል *ለሰሚዕ እጽብ ለሰሚው አስደናቂ *ብላዕ በሐፈ ገጽከ ጥረህ ግረህ ብላ *አክብር አባከ ወእመከ አባትና እናትህን አክብር *ተፋቀሩ በበይናቲከሙ እርስ በርሳችሁ ተዋደዱ *ኀላፊ ንብረት፣ክመ ጽላሎት ሀብት እንደ ጥላ አላፊ ነው *እምነ ረሃብ የኄይስ ኩይናት ከረሀብ ጦርነት ይሻላል። *ለዘየአምን ኩሉ ይትከሃል ለሚያምን ሁሉ ይቻላል *ሕማማ ለዐይን ርዕየተ ጸላኢ ያይን በሽታዋ ጠላትን ማየቷ *እለ ከርሦሙ አምላኮሙ ሆድ አምላኪዎች *ሀብ ለኩሉ ለዘሰአለከ ለለመነህ ሁሉ ስጥ *በቁስለ ዚአሁ ሀዮነ ቁስለነ በእርሱ ቁስል እኛ ተፈወስን *አኮ ለዘሮጸ ባህቱ ለዘበደረ ለሮጠ አይደለም ለቀደመ እንጅ *አፍቅር ቢጸከ ከመ ነፍስከ ባልንጀራህን እንደራስህ ውደድ *እስመ ፍቅር ከመ ሞት ጽንእት ፍቅር እንደሞት ጽኑ ናት። *ሕይወት ወሞት ውስተ እደ ልሳን ህይወትም ሞትም በአፍ ይመጣሉ *መኑ ከመ አምላከነ? እንደ እግዚአብሔር ያለ ማን አለ? *አኮ በሲበት አላ በአእምሮ በሽበት አይደለም፤በማስተዋል እንጅ *ህብ ፍኖተከ ለእግዚአብሔር መንገድህን ለእግዚአብሔር አደራ ስጥ *ሀቡ ዘነጋሢ ለነጋሢ፤ወዘተረፈእግዚአብሔር ለእግዚአብሔር የቄሳርን ለቄሳር፤የእግዚአብሔርን ለእግዚአብሔር ስጡ። ...
ግዕዝና አማረኛ ዓለም አቀፍ ናቸው
ግዕዝና አማረኛ ዓለም አቀፍ ናቸው ስንል ይኸው በማስረጃ ነው። ጥንታዊቷ ፊደላችን ♥ አ ቦ ጊ ዳ ................ የኢትዮጵያ ታሪክ ቅርስ በዓለም ሁሉ የአበራ የተመዘገበ ነው እኛ የእኛውን ሀብታችን እንጠብቅ።ትንሽ ስለአማርኛ ቋንቋ ... መራራ ሃቅ 1. የአማርኛ ቋንቋ ከክርስቶስ ልደት በፊት ነበረ። በሁለተኛው ክፍለ ዘመን (200-130 ዓ . ዓ ) የግብጹ ንጉሥ ጥሊሞስ 7 ኛ መምህር የነበረውና የግሪክ መልክዓ ምድር ተመራማሪ አጋታርከስ በሰሜን ኢትዮጵያ የሚኖሩ ህዝቦች የሚናገሩት የአማርኛ ቋንቋ እንደሆነ ጽፏል፥ተረጋግጧል።በአርኪኦሎጂያዊ ምርመራ ሂደት በአማርኛ የተቀረጹ ጥንታዊ የድንጋይ ላይ ጽሁፎች ተገኝተዋል ( አምሳሉ 1976) 2. አማራዎች ከ 3 ሺህ አመት በፊት በአማርኛ ቋንቋ ለንግሥት ሳባ ልጅ " ምኒልክ " ብለው ስም ከአወጡ በኋላ ይሁን በፊት በርካታ ስሞችን በአማርኛ እናገኛለን። 3. አሜሪካዊው ቤንደር በ 1966 ዓ . ም በኦክስፎርድ ዩኒቨርስቲ ባሳተመው /Language in Ethiopia/ በሚሰኘው መፅሐፉ በ 9 ኛው መቶ ክፍለ ዘመን አማርኛ በቤተ - አምሓራ እንደተስፋፋ ጽፏል።ኩፐር የተባለው ጽሐፊ በንጉስ ላሊበላ ዘመን አማርኛ ከአገወኛ ጋር በህዝቡ ይነገር ነበር ብሏል። 4. በ 12 ኛው መክዘ አጼ ይኩኖ አምላክ ዘመን ዐማርኛ ቋንቋ ፈጽሞ ሠለጠነ ፤ ያማረ የተወደደ ፥ ጉሮሮ የማያንቅ ፥ ለንግግር የማያውክ ሁኖ ስለ ተገኘ ፣ የቤተ መንግሥት ቋንቋ ሆነ።ለአማርኛ ዕድገት የ...

Comments
Post a Comment